BilalMicrofinance

የዕድገት ምዕራፍ ጅማሮ!
ከማረጋጋት ወደ ዕድገት፡ FROM STABILIZATION TO GROWTH!
***
ቢላል ማይክሮፋይናንስ የ2025/26 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የ2026/27 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይት የተቋሙ ማኔጅመንት አባላት እና ሁሉም ቅርንጫፍ ሥ/አስኪያጆች በተገኙበት አካሂዷል፡፡
በተጠናቀቀው የ2025/26 በጀት ዓመት ተቋሙን የተረጋጋ በማድረግ ረገድ አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል፡፡ በበጀት ዓመቱ:
• የተጣራ ቁጠባ ብር 55.6 ሚሊዮን ደርሷል፡፡
• ብር 52 ሚሊዮን ብድር (ፋይናንስ) አሰራጭቷል፡፡
• አጠቃላይ የተቋሙ ሃብት ብር 82.8 ሚሊዮን ደርሷል፡፡
• አጠቃላይ የደንበኞች ቁጥር 8,800 ደርሷል፡፡
• በአሁኑ ሰዓት ሁሉም የተቋሙ ቅርንጫፎች ወደትርፋማነት ተሸጋግረዋል፡፡
በቀጣዩ በጀት ዓመት:
• የተጣራ ቁጠባ ብር 112.8 ሚሊዮን ለማድረስ
• ብር 121.3 ሚሊዮን ብድር ለማሰራጨት
• የደንበኞች ቁጥር 20,433 ለማድረስ በዕቅድ ተቀምጧል፡፡
በሌላ በኩል
• የሠው ሃብት ልማት ሥራ፣
• የዲጂታል ቴክኖሎጂ ትግበራ፣
• ካፒታል ማሰባሰብ፣
• ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለን ግንኙነት ማጠናከር የቀጣይ በጀት ዓመት ቁልፍ ተግባራት መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ቢላል ማይክሮፋይናንስ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ለመመዝገብ ቅድመ-ሁኔታዎች አጠናቆ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡
አንድ ተቋም ከምስረታ ጀምሮ ወደ ትርፋማነት እስኪሸጋገር ድረስ ራሳቸውን የቻሉ ተፈጥሯዊ ዑደቶችን ያልፋል፡፡
የተከበራችሁ የቢላል ማይክሮፋይናንስ ባለአክሲዮኖች እና ደንበኞች እንዲሁም ሠራተኞች!
ቢላል ማይክሮፋይናንስ በአሁኑ ሰዓት የመረጋጋት (stabilization) ዑደትን አልፎ የዕድገት ምዕራፍ መጀመሩን በይፋ ያበስራል፡፡
***
ቢላል ማይክሮፋይናንስ
ከሁሉም ለሁሉም!